Zehabesha Telegram Channel

Ethiopian News

View in Telegram

Recent Posts

ፑቲን ስለሽብር ጥቃቱ የተናገሩትን በ3 መረጃዎች ላይ እዚህ ይመልከቱ https://www.youtube.com/watch?v=EcnYBXhVEZk
በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በሚገኘው ኮርኩስ ሲቲ ሆል አዳራሽ የሙዚቃ ድግስ ላይ የሽብር ጥቃት ፈፅመው ከ100 በላይ ሰዎችን የገደሉ ጥቃት ፈፃሚዎችን መያዟን ሩሲያ አስታወቀች::
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር በትግራይ ጦርነት የተማረኩ 112 የመከላከያ አባላትን ከእስር ለቀቅኩ አለ::

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት https://youtube.com/@TheEthiopia13?si=HHtGSEL0WH3ls85J
ዶክተር በሃይሉ ሀይሉ ከከፍታ ቦታ በመውደቅ በአካላቸው ላይ በተከሰተ ጉዳት ህይወታቸው ማለፉን የዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል የአስክሬን የምርመራ ውጤቱ እንዳረጋገጠ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራውን የቀጠለ ሲሆን ከከፍታው የወደቁበትን ሁኔታና ሌሎች ተያያዥ የምርመራ ውጤቶች ሲጠቃለሉ ለህዝብ ግልፅ እንደሚደረጉ አስታውቋል፡፡
***
የሰርጀሪ ህክምና ባለሞያ የሆኑት ዶክተር በሀይሉ ሀይሉ መጋቢት 8 ቀን 2016 ዓ ም በዕለተ እሁድ ሊነጋጋ ሲል ስፖርት ለመስራት ከቤት ወጥተው እንዳልተመለሱ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ሲገለፅ ቆይቷል።
ፖሊስ መረጃው ከደረሰው ሰዓት ጀምሮ ባደረገው ማጣራት የሟች ዶክተር በሀይሉ ሀይሉ አስከሬን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ከቦሌ ሚካኤል ወደ ሳሪስ አቦ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኝ ቀጠና 3 በተለምዶ ማሞ ድልድይ ስር ወድቆ በመገኘቱ በወቅቱ አስከሬኑ ተነስቶ የአሟሟታቸውን ምክንያት ለማወቅ ለአስክሬን ምርመራ ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል እዲሄድ ተደርጓል ፡፡ ከሆስፒታሉ የተገኘው የአስክሬን ምርመራ ውጤት እንደሚያስረዳው ከከፍታ ቦታ በመውደቅ በአካላቸው ላይ በተከሰተ ጉዳት ህይወታቸው ማለፉን የአስክሬን የምርመራ ውጤቱ ይገልፃል፡፡ ሟች ዶ/ር በይሉ ሐይሉ ከከፍታው ላይ ቁልቁል ወደ ገደሉ በመውረድ አካላቸው ድንጋይ ላይ ስላረፈ በጭንቅላታቸው፤ በእግራቸው በጀርባ አጥንታቸውና በውስጥ የሰውነታቸው አካላት ላይ በደረሰባቸው ከፍተኛ ጉዳት ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ከሆስፒታሉ የተገኘው የአስክሬን የምርመራ ውጤቱ ያብራራል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራውን የቀጠለ ሲሆን ከከፍታው የወደቁበትን ሁኔታና ሌሎች ተያያዥ የምርመራ ውጤቶች ሲጠቃለሉ ለህዝብ ግልፅ የሚደረጉ መሆናቸውን ፖሊስ አስታውቋል፡፡ ፖሊስ በዶክተር በሃይሉ ሀይሉ አሟሟትን የተሰማውን ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸውና ለሙያ አጋሮቻቸው መፅናናት እንዲሰጣቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡
በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በተዘጋጀ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ በደረሰ ድንገተኛ ጥቃት በርካታ ሰዎች ተገደሉ።

ጥቃቱ የተፈጸመው በሞስኮ በሚገኘው ኮርኩስ ሲቲ ሆል አዳራሽ ውስጥ እየተካሄደ በነበረ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ነው::

https://youtube.com/@TheEthiopia13?si=HHtGSEL0WH3ls85J
በሊቢያ የስደተኞች የጅምላ መቃብር መገኘቱን የመንግሥታቱ ድርጅት አስታወቀ


ስደተኞቹ የሊቢያን በረሃ ሲያቋርጡ ሳይሞቱ እንዳልቀረ ይታመናል

ሊቢያ ውስጥ ቢያንስ የ65 ስደተኞችን አስከሬኖች ያያዘ የጅምላ መቃብር መገኘቱን ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (አይኦኤም) አስታወቀ።
ስደተኞቹ የሞቱበትን ሁኔታ እና የየት አገር ዜጎች ስለመሆናቸው አስካሁን የታወቀ ነገር እንደሌለ ድርጅቱ ገልጾ፣ ነገር ግን በሊቢያ በረሃ በኩል ወደ ሜዲትራኒያን ባሕር በድብቅ ሲወሰዱ ሳይሞቱ እንደማይቀሩ ይታመናል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አንድ አካል የሆነው ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት በተገኘው የጅምላ መቃብር “በጥልቅ መደንገጡን” ገልጿል።

https://youtube.com/@TheEthiopia13?si=HHtGSEL0WH3ls85J

@BBC
በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመጡ የቀን ሰራተኛ ናቸው የተባሉ ከቁጥጥር ስር ከዋሉበት መለቀቃቸው ተሰማ::
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የብዙሀን መገናኛ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ሊቀ መምህራን ፋንታሁን ሙጬ ከሀገር መሰደዳቸው ተሰማ::

ተጨማሪ መረጃ ይዘን እንመለሳለን::
ሕዝብን ማታለል፣ እንደቀድሞ እየዋሹ መኖር የማይቻልበት ደረጃ ተደርሷል። ከአዲስ አበባ ማኀበራዊ ንቅናቄ (#አማን) የተሠጠ መግለጫ በአዲስአበባ ሳር ቤት አካባቢ በአማንና አራዳ የመንግስት ሠራተኞች ክፍል መጋቢት 11/2016 ዓ.ም በሠራተኞች ማጓጓዣ (public bus) ላይ የተወሰደውን ጥቃት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሊያስተባብል ሞክሯል። ይህ ከማኀበረሰቡ የተነጠለ፣ የሕዝብ ጠላት ለሆነው…
ሕዝብን ማታለል፣ እንደቀድሞ እየዋሹ መኖር የማይቻልበት ደረጃ ተደርሷል።

ከአዲስ አበባ ማኀበራዊ ንቅናቄ (#አማን) የተሠጠ መግለጫ

በአዲስአበባ ሳር ቤት አካባቢ በአማንና አራዳ የመንግስት ሠራተኞች ክፍል መጋቢት 11/2016 ዓ.ም በሠራተኞች ማጓጓዣ (public bus) ላይ የተወሰደውን ጥቃት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሊያስተባብል ሞክሯል። ይህ ከማኀበረሰቡ የተነጠለ፣ የሕዝብ ጠላት ለሆነው አገዛዝ ወንበር ጠባቂ የሆነ ክፍል በቀን የተፈጸመን ጥቃት፣ ሕዝብ የተመለከተውን ክስተት አልተፈጸመም ብሎ ሊክድ ሞክሯል።

በመሠረቱ ጥቃቱና እንቅስቃሴው ለመጀመሪያ ጊዜ የተከናወነ እንዳልሆነ ፖሊስ ጠንቅቆ ያውቃል። ሜክሲኮ ፌደራል ፖሊስ ዋና ቢሮ አጠገብ የአማን ወረቀት መበተኑ እንዴት እንዳስደነገጠው እናውቃለን። አራት ኪሎ አማን ፋኖንና ሌሎች አጋሮቹን ጨምሮ ኢትዮጵያ ተነሽ ማለታችንን ተከትሎ ፖሊሶችና የመከላከያ አባላቱ ላይ ምን አይነት እርምጃ እንደወሰደ እኛም እናውቃለን። እነሱም ያውቃሉ።

ገለልተኛና ሕዝባዊ መሆን የነበረበት ይህ አካል ለመጣው ለሄደው ሁሉ መንበርከኩን ቀጥሎ ለአዳነች አበቤ ፀረ-ሕዝብ አገዛዝ ጉልበቱ እስኪላጥ ተንበርክኮ ጥቂት የቀረችውን ስሙን አጥቶአል። ዛሬ ለስሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ተብሎ በእውነታው ግን ለቅኝት የሚመደቡ ተራ ፖሊሶችን ሳይቀር በብሄረሰብ ኮታ እየመደበ የሚገኝበት የአለመተማመን ደረጃው በአፍጢሙ ሊደፋው፣ የፍርሀት መጠኑ በአናቱ ሊተክለው የደረሰ አካል ሆኗል።

የሕዝብን ቁጣ፣ የአዲስ አበቤን መነዴት በክህደታቹ ልትሸፍኑት አትችሉም።ዛሬ የደረስበት መንገፍገፍ፣ የደረስንበት ቁጣ ቢሯችሁ ድረስ እንድንገባ አድርጎናል። ለነገ ታሪካቹ በእውነት የምታስቡ ከሆነ አይን ያወጣ ውሸታችሁን ትታችሁ ከህዝባችሁ ጎን ቁሙ፣ ሀገር ለማፍረስ ከሚተጋ አረመኔ ስርዓት አትተባበሩ። ይህ ብቻ ነው ለጥፋታቹ ስርየት፣ ለኃጢአታችሁ ንስሃ የሚሆነው። ከዚህ ውጭ መንገድ የለም። ወይ ሕዝባዊነት፣ ወይንም ሕዝብና ሀገርን ክዶ ከአገዛዙ ጋር መቆም።

ይህን የካዳችሁትን የመንግስት ሠራተኛውን ቁጣ የንቅናቄያችን የሠራተኛ ክፍል በቀጣይነት ምን ደረጃ እንደደረሠ ሊያሣይ ቃል ይገባል።

የአዲስ አበባ ማኀበራዊ ንቅናቄ (#አማን)

ሕዝባዊነት ያሸንፋል።
ሀሰተኛ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳሰበ። *** የከተማችን ሰላም መሆን እንቅልፍ የነሳቸው አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች የተለያዩ የሀሰት መረጃዎችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ስጋት ላይ ለመጣል በቻሉት መጠን ሁሉ ጥረቶችን እያደረጉ ይገኛሉ። እነዚህ አካላት በተደጋጋሚ ጊዜ በመዲናችንን ሰላም እንደሌለና ህዝቡ ስጋት ውስጥ እንወደቀ ለማስመሰል…
ከንግድ ባንክ ብር የወሰዱ ተማሪዎች በገንዘቡ ላፕቶፕ እና ስማርት ስልክ በብሩ በመግዛታቸው አሁን ወደ ባንኩ ብሩን ለመመለስ መቸገራቸው ተሰማ::
ተማሪዎቹ በጭንቀት ውስጥ መሆናቸውም ተሰምቷል::
አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በግል ጉዳያቸዉ ምክንያት በኮሚሽነርነት ላለመቀጠል ያቀረቡት ጥያቄ በመንግስት ተቀባይነት በማግኘቱ የኮሚሽነርነት ቦታቸዉን መልቀቃቸው ተሰማ:: በምትካቸው አቶ ተመስገን ጥላሁን የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል::
በሞጆ ከተማ 2 መቶ የሚሆኑ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ገንዘብ ካልከፈላችሁ አታልፉም በሚል መቆማቸዉ ተሰማ፡፡


2 መቶ የሚሆኑ እነዚህ የአሸዋ ገልባጭ የሲኖትራክ አሽከርካሪዎች እንደ ገለፁት በየቦታዉ ያለአግባብና ባልተለመደ መልኩ እንድንቆሙና ገንዘብ እንድንከፋል ተደርገናል ነው ያሉት።
ከዚህ በፊት አንድ ገልባጭ መኪና ከቦታው ጭኖ ሲወጣ እዛው በደረሰኝ የሚከፍል ነበር ተብሏል፡፡
አሁን ግን በየቦታው የኮቴ እየተባለ በሚሊሻ አካላት ያለ ሰዓት እያስቆሙ በግድ ገንዘብ እንድንከፍል እያደረጉ ነው ብለዋል።
በዚህም አልከፍልም ያሉ አሽከርካሪዎች ላይ በመንግሥት የሚሊሺያ አባላት ድብደባ ፣ እስር፣ እንዲሁም የመኪናቸው ጎማ እየተመታና ለተለያዩ እንግልት እየተዳረግን ነው ብለዋል ።
አሺከርካሪዎቹ እንደገለፁት እንዲህ ያለው ተግባር በፊትም አልፎ አልፎ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን በግልፅ እንዳንሰራ ወጥተን እንዳንገባ እንዳንቀሳቀስ ሆነናል ነው የሚሉት ።
በመጨረሻም የሚመለከተው አካል አስቸኳ መፍትሄ ይስጠን ሲሉም ጠይቀዋል።
በልዑል ወልዴ

@ኢትዮ ኤፍኤም

View in Telegram

Telegram Channel